Telegram Group & Telegram Channel
ራስን መሆን ይውደም!

Don't be yourself
_+++_

በጉዳዩ ላይ ከመፃፌ ከብዙ ቀናት በፊት የተወሰኑ መፅሐፍቶችን ለማንበብ ፥ አንዳንድ ሌክቸሮችን ለማዳመጥ ሞክሬ ነበር። አንዳንድ የሐገራችን ግላዊነትን ወይም ራስን መሆንን ለማበረታታት የተፃፉ ፅሑፎች ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌላቸውን ነገሮች በመተረክ ሐሳባቸውን ይስታሉ፤ አንዳንድ ያልኩት በጉዳዩ መረዳት ይኖራቸዋል ብዬ ያሰብኳቸውን እንጂ ብዛታቸውስ የትዬለሌ ነው። ለአብነት ከባዶ ላይ ያዘገነን "ከባዶ ላይ መዝገን" የተባለው መፅሐፍ ማንሳት ይቻላል። ስምን መልአክ አወጣው መሠል..¿

ከመች ጀምሮ እንደሆነ ጠንካራ ትውፊት ወዳላቸው ሐይማኖቶች እንደገባ አላውቅም። ሰባኪው ፣ ዳዒው ራስን ስለመሆን ረጅም ስብከት ያካሄዳል። በእለት ተእለት የጥቅስ አጠቃቀማችን ውስጥ "Just be yourself , follow your own star ,Existence wants you to be you...ወዘተርፈ በመሰሉ አባባሎች ራሳችንን ለመቅረጽ ደፋ ቀና ማለት ከጀመርን ውለን ሰነበትን። በእርግጥ "ራስን መሆን" ከላይ መልካም ነገር ይመስል ይሆናል፤ በተለይ በጥቅስነት ድባቡ። ግን የተወሰኑ ጥያቄዎችን በመመለስ ስለጉዳዩ ጥቂት መንገድ ለመጥረግ ልሞክር ፤ ለምን ራስን መሆን መውደም አለበት?

፨ ራስን መሆን ምንድነው? ፨ ጥቅሙ ወይስ ጉዳቱ? ፨ እንደ እስልምና? ፨

🔑 ራስን መሆን ምን ማለት ነው ?

ራስን መሆን ማለት ነፃነት ማለት ነው በሌላ አማርኛ። ወይም ደግሞ በፍልስፍናዊ የቃል ፍቺው ግለሰባዊነት(Individualism) ማለት ይሆናል። ራስን መሆን ሌሎችን አለመሆን ማለትም ነው። ከሕላዊነት (Existentialism¹) ፍልስፍና ጋርም የተጋመደ ነው።² አንድነት ራስን ባለመሆን ውስጥ የሚጠነክር ነው። ልዩነት ደግሞ ራስን በመሆን ውስጥ። ብዙዎች ራስን መሆንን በመነጠል ከሚገኝ ስኬት ጋር ያገናኙታል። ያ የሐይማኖትም ምክር ነው። ግላዊነት እና ራስን መሆን የተነሳበት መንፈስ ግን ሌላ ነው።

እንዲህ የሚል ድምዳሜ ከተለያዩ ፀሐፊያን እና የሕላዊነት ፍልስፍና አቀንቃኞች መፅሐፍት እንጠቁም።ራስን መሆን፥ ራስን በራስ ሕግ መምራት ማለት ነው። ማለትም ማንም የበላይ አዛዥ በተለይም የሐይማኖት መሪ ወይም መምህር ሳያስፈልግ ልናደርጋቸው የምንፈልጋቸውን ነገሮች ኹሉ በራሳችን ሕግ ተመርተን ማድረግ እንችላለን። መሠረታዊ የሥነ ምግባር መርሕ የሚመነጨው ከማንም ሳይኾን ከራስ ወይም ከግለሰብ ብቻ ነው የሚል። ምላሹንም የሚያገኘው ከራሱ ብቻ ነው። ስለዚህም ድርጊቶቹ በራሱ ምርጫ ላይ የተደገፉና የራሱን ፍላጎትና ደስታ ብቻ የሚወስኑ ናቸው³።

ጉዳዩ እድገት ነበረው። መነነሻው ከፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ ጋር የተገናኘ ነው።የአእማዶቹ (sola) ብቻዎች በዚህ የተቃኙ ነበሩ።በራስ መተርጎም ፣ የግል አዳኝነት...የመሰሉ እሳቤዎች ከዚህ ጋር የተገናኘ ገመድ አለው። ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ በኋላ ግን እየተቀየረ ሄዶ "ሌላውን ሰው የማይጎዳ እስከኾነ ድረስ የምትፈልገውን ማንኛውንም ነገር ማድረግ መብት አለህ" ወደሚል አሳብ አደገ። ከ2ኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ብዙ የፍልስፍና ሐሳቦች መወለዳቸውን ተከትሎም በሚመስል መልኩ ራስን መሆን ወይም "ግለሰባዊነት" ሌላ ትርጉም ይዞ መጣ። "ዓለም ሁላችንም በተለያየ መንገድ እንደምናያት አድርገን እንድንገልጻት መብት ይኑረን" ወደሚል።

ከጉዳዩ ጋር ስሙ የማይጠፋው ፈረንሳያዊው ፈላስፋ ዣን ፖሎ ሳርተር (Jean paul Sartre) እንዲህ ይላል ❝የሰው ልጅ መሠረታዊ ዓላማ ምን እንደሆነ በጥሩ ሁኔታ ለመረዳት የሚያስችለን አገላለጽ ሰው ማለት አምላክን (አሏል ፥ እግዚአብሔር )ን የመሆን ዓላማ ያለው ፍጡር ማለት ነው❞⁴ብሏል። ጇኬስም ያለፉትን የአምስት መቶ አመታት የምዕራባውያንን የአኗኗር ባሕል ወደ ኋላ መለስ ብሎ በጥንቃቄ ከቃኘ በኋላ የሰው ልጅ ትልቁ ዕውን ማድረግ የሚፈልገው ዓላማ ነጻ መውጣት ፣ ከኹሉም ዓይነት ቁጥጥር መላቀቅ ወይም ከማንኛውም የበላይ ሥልጣንና ፈቃድና ፍላጎት ውጭ መኾን ነው በማለት አስቀምጧል።⁵

ቀጣዮቹ ስንኞች አሜሪካዊው ባለቅኔ Walter Whitman "The Song of Myself በሚል ከፃፈው ግጥም ውስጥ የተወሰዱ ናቸው።
ግርጌ ላይ በአማርኛ ተሞክሯል እናንተም በተመቻችሁ መንገድ ተርጉሙት

«Do I contradict my self?
Very well then....I contradict myself;
I am large .... I contain multitudes »⁶

አሜሪካዊው ባለቅኔ Walter Whitman "Leaves of the Grass (1855) በሚለው መፅሀፉ ውስጥ " The Song of Myself" በተባለው ግጥም ግላዊነትን (Individualism) በሰፊው ይሰብካል።

በአጭሩም ግለሰባዊነት ትወይም ራስን መሆን ማለት ራስን በራስ ወይም በስሜት ሕግ መምራት ማለት ነው። ብዙም የማንሳት ሐሳቤ ባይሆንም የመፅሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ የግለሰባዊነት አራማጅ ነበር የሚሉ ብዙ አሉ። የቤተመቅደሱን መጋረጃ ቀድዶ እያንዳንዱ ሰው ከፈጣሪው ጋር አንድ ለአንድ (one to one ) እንዲገናኝ አድርጓል ይላሉ። የራሳቸው ጉዳይ...!

***

🔑ራስን መሆንና ግለሰባዊነት ጥቅሙ ወይንስ ጉዳቱ ?

ይሄን ጉዳይ ለማሣጠር ልሞክር። አንድ የተሳሳተ ሐሳብ ብዙውን ጊዜ ይነሳል። ግለሰባዊነት ማለት ብቻ ከመሆን ጋር እየተነሳ ለማወዛገብ መንገድ ይሆናል።ብቻ መሆን ማለት ራስን መሆን ማለት አይደለም። ሰው ለተፈኩር ስለተገለለ ፣ ብቻውን ኑሮውን ስለገፋ ራሱን እየሆነ ነው ፣ ነፃ ነው ነው ማለት ፤ የሕብረትን ትርጉም እና ቦታ አለማወቅ ነው።

ብቻ መሆን ጥቅም አለው። አንግሥ ማርቲን « በሕይወትህ እጅግ መልካም የሚባሉ ነገሮች የሚከሰቱልህ ብቻህን ስትሆን ነው» ትላለች። እውነት ነው። ግን ብቻ መሆንን መምረጥ ማለት ብቸኛ መሆን ማለት አይደለም። እንደውም ሳርተር «ለብቻህ ስትሆን ብቸኛ ከሆንክ መጥፎ ጀማ ውስጥ ነህ» ይላል። ብቻነት እና ብቸኝነትን ነጣጥለን ማየት አለብን። ግለሰባዊነት የሚፈጥረው ብቻነትን ሳይሆን ብቸኝነትን ነው። ኡመር ረ.ዐ የተባለ የነብዩ ባልደረባ እንዲህ ብሏል ''ከመጥፎ ሰዎች ከመቀላቀል ለብቻ መሆን እረፍት ነው'''።⁷ ዑመር በሕብረት ወይም በአንድነት ወይም በፍልስፍና አጠራሩ (Collectivism ) የሚያምን ታላቅ ሐዋርያ ነው። ሕብረት የግለሰባዊነት ፅንፍ ነው።

ታላላቅ አሳቢያን የሚስማሙበት ነገር ራስን መሆን(ግለሰባዊነት) የሚሰጠው ውጤት ራስን ማጣት(ቀውስ) ነው ወደሚል መንገድ ነው። ሕልም ተፈርቶ የሚል ብሒል ለሚያቀርብልኝ ሰው የምሰጠው «አያ በሬ ሆይ! ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ» የሚል ነው። የተቻለውን ያሕል ሐብት ማፍራትም እንዲሁ እንደ ግለሰባዊነት የነፃነት መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል። በዚህም ሳቢያ ነፃነት በፉክክር ላሸነፉት ብቻ የምትሰጥ ሽልማት ነች ማለት ነው። ሰው ባለው መጠን እንጂ በማንነቱ ብቻ ግለሰብነቱን የማይቀዳጅ ባርያ ሆኖ ይገኛል ማለት ነው። አገኘሁ ብሎ መቀማት እንዲህ ካልሆነ...?!



tg-me.com/comparativereligious/1073
Create:
Last Update:

ራስን መሆን ይውደም!

Don't be yourself
_+++_

በጉዳዩ ላይ ከመፃፌ ከብዙ ቀናት በፊት የተወሰኑ መፅሐፍቶችን ለማንበብ ፥ አንዳንድ ሌክቸሮችን ለማዳመጥ ሞክሬ ነበር። አንዳንድ የሐገራችን ግላዊነትን ወይም ራስን መሆንን ለማበረታታት የተፃፉ ፅሑፎች ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌላቸውን ነገሮች በመተረክ ሐሳባቸውን ይስታሉ፤ አንዳንድ ያልኩት በጉዳዩ መረዳት ይኖራቸዋል ብዬ ያሰብኳቸውን እንጂ ብዛታቸውስ የትዬለሌ ነው። ለአብነት ከባዶ ላይ ያዘገነን "ከባዶ ላይ መዝገን" የተባለው መፅሐፍ ማንሳት ይቻላል። ስምን መልአክ አወጣው መሠል..¿

ከመች ጀምሮ እንደሆነ ጠንካራ ትውፊት ወዳላቸው ሐይማኖቶች እንደገባ አላውቅም። ሰባኪው ፣ ዳዒው ራስን ስለመሆን ረጅም ስብከት ያካሄዳል። በእለት ተእለት የጥቅስ አጠቃቀማችን ውስጥ "Just be yourself , follow your own star ,Existence wants you to be you...ወዘተርፈ በመሰሉ አባባሎች ራሳችንን ለመቅረጽ ደፋ ቀና ማለት ከጀመርን ውለን ሰነበትን። በእርግጥ "ራስን መሆን" ከላይ መልካም ነገር ይመስል ይሆናል፤ በተለይ በጥቅስነት ድባቡ። ግን የተወሰኑ ጥያቄዎችን በመመለስ ስለጉዳዩ ጥቂት መንገድ ለመጥረግ ልሞክር ፤ ለምን ራስን መሆን መውደም አለበት?

፨ ራስን መሆን ምንድነው? ፨ ጥቅሙ ወይስ ጉዳቱ? ፨ እንደ እስልምና? ፨

🔑 ራስን መሆን ምን ማለት ነው ?

ራስን መሆን ማለት ነፃነት ማለት ነው በሌላ አማርኛ። ወይም ደግሞ በፍልስፍናዊ የቃል ፍቺው ግለሰባዊነት(Individualism) ማለት ይሆናል። ራስን መሆን ሌሎችን አለመሆን ማለትም ነው። ከሕላዊነት (Existentialism¹) ፍልስፍና ጋርም የተጋመደ ነው።² አንድነት ራስን ባለመሆን ውስጥ የሚጠነክር ነው። ልዩነት ደግሞ ራስን በመሆን ውስጥ። ብዙዎች ራስን መሆንን በመነጠል ከሚገኝ ስኬት ጋር ያገናኙታል። ያ የሐይማኖትም ምክር ነው። ግላዊነት እና ራስን መሆን የተነሳበት መንፈስ ግን ሌላ ነው።

እንዲህ የሚል ድምዳሜ ከተለያዩ ፀሐፊያን እና የሕላዊነት ፍልስፍና አቀንቃኞች መፅሐፍት እንጠቁም።ራስን መሆን፥ ራስን በራስ ሕግ መምራት ማለት ነው። ማለትም ማንም የበላይ አዛዥ በተለይም የሐይማኖት መሪ ወይም መምህር ሳያስፈልግ ልናደርጋቸው የምንፈልጋቸውን ነገሮች ኹሉ በራሳችን ሕግ ተመርተን ማድረግ እንችላለን። መሠረታዊ የሥነ ምግባር መርሕ የሚመነጨው ከማንም ሳይኾን ከራስ ወይም ከግለሰብ ብቻ ነው የሚል። ምላሹንም የሚያገኘው ከራሱ ብቻ ነው። ስለዚህም ድርጊቶቹ በራሱ ምርጫ ላይ የተደገፉና የራሱን ፍላጎትና ደስታ ብቻ የሚወስኑ ናቸው³።

ጉዳዩ እድገት ነበረው። መነነሻው ከፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴ ጋር የተገናኘ ነው።የአእማዶቹ (sola) ብቻዎች በዚህ የተቃኙ ነበሩ።በራስ መተርጎም ፣ የግል አዳኝነት...የመሰሉ እሳቤዎች ከዚህ ጋር የተገናኘ ገመድ አለው። ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ በኋላ ግን እየተቀየረ ሄዶ "ሌላውን ሰው የማይጎዳ እስከኾነ ድረስ የምትፈልገውን ማንኛውንም ነገር ማድረግ መብት አለህ" ወደሚል አሳብ አደገ። ከ2ኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ብዙ የፍልስፍና ሐሳቦች መወለዳቸውን ተከትሎም በሚመስል መልኩ ራስን መሆን ወይም "ግለሰባዊነት" ሌላ ትርጉም ይዞ መጣ። "ዓለም ሁላችንም በተለያየ መንገድ እንደምናያት አድርገን እንድንገልጻት መብት ይኑረን" ወደሚል።

ከጉዳዩ ጋር ስሙ የማይጠፋው ፈረንሳያዊው ፈላስፋ ዣን ፖሎ ሳርተር (Jean paul Sartre) እንዲህ ይላል ❝የሰው ልጅ መሠረታዊ ዓላማ ምን እንደሆነ በጥሩ ሁኔታ ለመረዳት የሚያስችለን አገላለጽ ሰው ማለት አምላክን (አሏል ፥ እግዚአብሔር )ን የመሆን ዓላማ ያለው ፍጡር ማለት ነው❞⁴ብሏል። ጇኬስም ያለፉትን የአምስት መቶ አመታት የምዕራባውያንን የአኗኗር ባሕል ወደ ኋላ መለስ ብሎ በጥንቃቄ ከቃኘ በኋላ የሰው ልጅ ትልቁ ዕውን ማድረግ የሚፈልገው ዓላማ ነጻ መውጣት ፣ ከኹሉም ዓይነት ቁጥጥር መላቀቅ ወይም ከማንኛውም የበላይ ሥልጣንና ፈቃድና ፍላጎት ውጭ መኾን ነው በማለት አስቀምጧል።⁵

ቀጣዮቹ ስንኞች አሜሪካዊው ባለቅኔ Walter Whitman "The Song of Myself በሚል ከፃፈው ግጥም ውስጥ የተወሰዱ ናቸው።
ግርጌ ላይ በአማርኛ ተሞክሯል እናንተም በተመቻችሁ መንገድ ተርጉሙት

«Do I contradict my self?
Very well then....I contradict myself;
I am large .... I contain multitudes »⁶

አሜሪካዊው ባለቅኔ Walter Whitman "Leaves of the Grass (1855) በሚለው መፅሀፉ ውስጥ " The Song of Myself" በተባለው ግጥም ግላዊነትን (Individualism) በሰፊው ይሰብካል።

በአጭሩም ግለሰባዊነት ትወይም ራስን መሆን ማለት ራስን በራስ ወይም በስሜት ሕግ መምራት ማለት ነው። ብዙም የማንሳት ሐሳቤ ባይሆንም የመፅሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ የግለሰባዊነት አራማጅ ነበር የሚሉ ብዙ አሉ። የቤተመቅደሱን መጋረጃ ቀድዶ እያንዳንዱ ሰው ከፈጣሪው ጋር አንድ ለአንድ (one to one ) እንዲገናኝ አድርጓል ይላሉ። የራሳቸው ጉዳይ...!

***

🔑ራስን መሆንና ግለሰባዊነት ጥቅሙ ወይንስ ጉዳቱ ?

ይሄን ጉዳይ ለማሣጠር ልሞክር። አንድ የተሳሳተ ሐሳብ ብዙውን ጊዜ ይነሳል። ግለሰባዊነት ማለት ብቻ ከመሆን ጋር እየተነሳ ለማወዛገብ መንገድ ይሆናል።ብቻ መሆን ማለት ራስን መሆን ማለት አይደለም። ሰው ለተፈኩር ስለተገለለ ፣ ብቻውን ኑሮውን ስለገፋ ራሱን እየሆነ ነው ፣ ነፃ ነው ነው ማለት ፤ የሕብረትን ትርጉም እና ቦታ አለማወቅ ነው።

ብቻ መሆን ጥቅም አለው። አንግሥ ማርቲን « በሕይወትህ እጅግ መልካም የሚባሉ ነገሮች የሚከሰቱልህ ብቻህን ስትሆን ነው» ትላለች። እውነት ነው። ግን ብቻ መሆንን መምረጥ ማለት ብቸኛ መሆን ማለት አይደለም። እንደውም ሳርተር «ለብቻህ ስትሆን ብቸኛ ከሆንክ መጥፎ ጀማ ውስጥ ነህ» ይላል። ብቻነት እና ብቸኝነትን ነጣጥለን ማየት አለብን። ግለሰባዊነት የሚፈጥረው ብቻነትን ሳይሆን ብቸኝነትን ነው። ኡመር ረ.ዐ የተባለ የነብዩ ባልደረባ እንዲህ ብሏል ''ከመጥፎ ሰዎች ከመቀላቀል ለብቻ መሆን እረፍት ነው'''።⁷ ዑመር በሕብረት ወይም በአንድነት ወይም በፍልስፍና አጠራሩ (Collectivism ) የሚያምን ታላቅ ሐዋርያ ነው። ሕብረት የግለሰባዊነት ፅንፍ ነው።

ታላላቅ አሳቢያን የሚስማሙበት ነገር ራስን መሆን(ግለሰባዊነት) የሚሰጠው ውጤት ራስን ማጣት(ቀውስ) ነው ወደሚል መንገድ ነው። ሕልም ተፈርቶ የሚል ብሒል ለሚያቀርብልኝ ሰው የምሰጠው «አያ በሬ ሆይ! ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ» የሚል ነው። የተቻለውን ያሕል ሐብት ማፍራትም እንዲሁ እንደ ግለሰባዊነት የነፃነት መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል። በዚህም ሳቢያ ነፃነት በፉክክር ላሸነፉት ብቻ የምትሰጥ ሽልማት ነች ማለት ነው። ሰው ባለው መጠን እንጂ በማንነቱ ብቻ ግለሰብነቱን የማይቀዳጅ ባርያ ሆኖ ይገኛል ማለት ነው። አገኘሁ ብሎ መቀማት እንዲህ ካልሆነ...?!

BY Ethio Muslim Apologetics


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/comparativereligious/1073

View MORE
Open in Telegram


Ethio Muslim Apologetics Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The S&P 500 slumped 1.8% on Monday and Tuesday, thanks to China Evergrande, the Chinese property company that looks like it is ready to default on its more-than $300 billion in debt. Cries of the next Lehman Brothers—or maybe the next Silverado?—echoed through the canyons of Wall Street as investors prepared for the worst.

For some time, Mr. Durov and a few dozen staffers had no fixed headquarters, but rather traveled the world, setting up shop in one city after another, he told the Journal in 2016. The company now has its operational base in Dubai, though it says it doesn’t keep servers there.Mr. Durov maintains a yearslong friendship from his VK days with actor and tech investor Jared Leto, with whom he shares an ascetic lifestyle that eschews meat and alcohol.

Ethio Muslim Apologetics from no


Telegram Ethio Muslim Apologetics
FROM USA